Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13088 -
Telegram Group & Telegram Channel
ቤተልሔም ፣ ዮርዳኖስና ቀራንዮ
በልደት ፣ በጥምቀትና በስቅለት
የአምላክ «መራቆት»
━━━✦༒༒✦━━━

መኑ ይሁበኒ ሥጋሁ ለኢየሱስ
ከመ እክድን ዕርቃኖ በልብስ
ለዘከደነ ዕርቃንየ በዮርዳኖስ

[ በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ማን በስጠኝ ?]

የዘፍጥረት መጽሐፍ ቀዳሚ መልእክት እንዲህ የሚል ነው «ወምድርሰ ሀለወት እምትካት ዕራቃ ☞ ምድር ግን ከቀድሞው ራቁትዋን ነበረች» ይህም ከአዝርዕት ከአትክል ከሰው የተራቆተች ሆና ባዶ ፣ ከንቱ ሆና ምድረ በዳ ነበረች ማለቱ ነው [ዘፍ ፩፥፪]

የፍጥረቱ አክሊልና የምድራችን ጌጥ ሆነን የተፈጠርነው እኛ የሰው ልጆችም ራቁትነታችን በብርሃን መጋረጃ የተሸፈነ ነበር ፤ ኋላ በበደላችን ምክንያት ከጸጋ ልጅነት ከአምላክ ባለሟልነት ስንርቅ ተራቁተን ቀረን እንጂ "አእመሩ ከመ ዕራቃኒሆሙ እሙንቱ ☞ ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ" እንዲል [ዘፍ ፫፥፮]

እግዚአብሔርን ለመምሰል ብርሃን ተጎናጽፎ ይኖር የነበረው ሰብእናችን በበደሉ ምክንያት ዕርቃናቸውን የሚኖሩ እንሰሳትን መሰለ።

አባ ጊዮርጊስ ይህን ርደት እንዲህ ገልጦታል ፦ “ምንት ውእቱ ተመስሎ እንስሳ ዘእንበለ ተከሥቶ ዕርቃኑ ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ሶበ ነፍጸ አጽፈ ብርሃን ዘላዕሌሁ ኀደጎ አጽፈ ብርሃን ⇨ በገነት ዛፎች መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ከመተየት በስተቀር እንስሳን መምሰል ምንድ ነው? የብርሃን ልብስ ከበላዩ ላይ በተገፈፈ ጊዜ የብርሃን መጐናጸፊየው ተለየው” (መጽሐፈ ምሥጢር)

በፍና ሠርክ በድምጸ ሰኮና ብእሲ ‘እንደምን ባለ አነዋዋር አላችሁ ይሆን ? በክብር ወይስ በኃሣር ? ’ እያለ ፈልጎ አገኘንና ስለመተላለፋችን ፈርዶ ከቀደመ ክብራችን አውርዶ ከገነት አስወጣን፤ ያን ጊዜ በጊዜአዊነትም ቢሆን ሐፍረት መክደኛ ዕርቃን መሸፈኛ አበጀልን! "ወገብረ እግዚአብሔር ለአዳም ወለብእሲቱ አእዳለ ዘማእስ ወአልበሶሙ … እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም።” [ዘፍ ፫፥፳፩]

ኋላ በምስጋና መብረቅ የተጋረደና በእሳት ደመና የተሸፈነ አምላክ ወልደ አምላክ የተስፋውን ቃል ለመፈጸም ከውድቀታችን ሊያነሳን ያን የተራቆተ ሥጋችንን ለበሰልን። የሚካኤል ሠራዊት በፍርኃት የገብርኤል ሠራዊት በመንቀጥቀጥ የሚያመሰግኑት እርሱ ዕርቃኑን በመካከላችን ተገኘ።

🍁 ወበቤተልሔም ወጽአ እምከርሰ እሙ ዕራቁ (በቤተልሔም ከእናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ)

መጽሐፍ "ዕራቅየ ወፃእኩ እምከርሠ እምየ" እንዳለ እኛን በሚመስልበት የተዋህዶ ግብር ከድንግል እናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ፤ ከመለኮቱ ሳይራቆት (ዕሩቅ ብእሲ ሳይሰኝ) ከሥጋ ልብስ ባዶ ሆኖ ተራቁቶ ፣ ክብሩን በፈቃዱ ትቶ በትህትና ወደምድራችን መጣ። ይህን ሥጋችንን ለብሶ የሰው ልጅ መባሉ ያንን የሰማይ ክብር እርሱን በጸጋ ለብሰን ትርሲተ ወልድ / የሥጦታ ልጆቹ ሊያሰኘን ነውና።

የመጽሐፉም ምስክርነት እንዲህ የሚል ነው "አሰረቶ መንኮብያቲሁ ወአስከበቶ ውስተ ጎል ወጠብለለቶ በጽርቅት ⇨ አውራ ጣቱን አሰረችው ፣ በግርግም አስተኛችው፣ በመጠቅለያም ጠቀለለችው” [ሉቃ ፪፥፯]

የ፲፭ ዓመቷ ገሊላዊት ብላቴና እናቱ ድንግል ማርያም በከብቶቹ ማደርያ ስትወልደው ለብኩርናው አውራ ጣቱን አሥራ፣ የተራቆተ ሰውነቱን በጨርቅ ጠቅላላ ፣ ለመኝታው ግርግም አሰናድታ ባላትና ባገኘችው ተቀበለችው። ይህም ለእኛ የተከፈለው ካሣ እረኞችም ምልክት እንዲሆናቸው በመልአኩ በኩል ‘እሱረ መንኮብያት ፣ ስኩብ ውስተ ጎል ፣ ጥብሉል በአጽርቅት (አውራ ጣቱ የታሠረ ፣ ከግርግም የተኛ ፣ በጨርቅ የተጠቀለለ) ሕፃን በበረቱ ታገኛላችሁ’ ተባሉ። [ሉቃ ፪፥፲፪]

ልጇን ጌታዬ የምትል ብቸኛዋ የፈጣሪ እናቱ የአምላክ ወላዲቱ ለዕርቃኑ መክደኛ የበለስ ቅጠል ስላገኘችበት ተኣምራታዊ መንገድ በቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ትውፊት
እንዲህ የሚል አብነት አለ
«በለሶን ዕፀ አእምሮ የሚባለው ነው፤ ይህ የገነት በለስ አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተው ቅጠሉን የለበሱት ኋላም የልደት ዕለት በተኣምራት መልአክ (ቅዱስ ገብርኤል) አምጥቶላት ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ለልጇ ለዳግማይ አዳም ሥግው ቃል ክርስቶስ ያለበሰችው ነው፤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው "ከደነቶ እሙ ቄጽለ በሰሶን" እንዳለው። ስለዚህ ምሥጢር ብዙዎች ብዙ ብለዋል!

ባለቅኔው ፦
በለሰ ገነት ለአዳም ወሔዋን መቲሮቶሙ
መንክረ ልደት አምላከ መንገሌሆሙ ሰሐበ
ወገብርኤልሃ ዜናዊ ቀጸበ
እንተ ከመዝሰ ግብር እምከመ ለአዳም ተውህበ
ወረከበት ሔዋን ዘኢተረክበ
ካዕበ ይስሐብ ኀቤሆሙ አበ
ለበለሰ ይምትርዎ ካዕበ

ደራሲው ፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ ዕሩያነ አካል ወአምሳል፥
አቅርንተ ነቢያት ሥላሴ ዘድምጽክሙ ወንጌል፥
ኢሳይያስ ጸርሐ ወይቤ ውስተ መካነ ላሕም ጎል፥
ገብርኤል አወፈየኒ ሕፃነ ማርያም ድንግል፥
በቆጽለ በለሶን ክዱን ወበጸርቅ ጥብሉል

🍁 ወበዮርዳኖስ ተጠምቀ በማይ ዕራቁ (በዮርዳኖስ ዕርቃኑን በውኃ ተጠመቀ)

ለኃጢዓታችን ሥርየት የሚሆን በግዕ ዘመስዋዕት፣ ለነፍሳችን ጠባቂዋ እረኛ ሊቀ ኖሎት፤ ወልዱ ለቡሩክ: ከሣቴ ብርሃን የዓለም መድኃኒት በባርያው በዮሐንስ እጅ እንዲጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ ሲገባ ከልብሱ መራቆቱን የአበው መጽሐፍ እንዲህ ይገልጣል

"አስተርአየ በውስተ ዮርዳኖስ እንዘ ክሡት ዕርቃኑ ለተጠምቆ ⇨ ለመጠመቅ ራቁቱን በዮርዳኖስ ባሕር ውስጥ ታየ" (መጽሐፈ ምሥጢር)

የዮርዳኖስ ጥምቀት የሁላችን ዕርቃን የተከደነበት ነው።

🍁 ወበቀራንዮ ሰቀልዎ ዲበ ዕፅ ዕራቆ (በቀራንዮ በእንጨት ላይ ዕርቃኑን ሰቀሉት)

አባ ጊዮርጊስ ስለዚህም እንዲህ ብሏል “ወበከመ ተከሥተ ዕርቃነ አዳም ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ከማሁ ተከሥተ ዕርቃነ ትስብእቱ ለመድኃኒነ ማዕከለ ጉባኤሆሙ ለማኅበረ እስራኤል ⇨ አዳም በገነት ዛፎች መካከል ርቃኑን እንደታየ እንደሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሰውነቱ በአይሁድ ጉባኤ መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ታየ” (መጽሐፈ ምሥጢር)
በደራስያኑም የመልክእ ምስጋና እንዲህ ተገልጧል፦

ሰላም ለዕርቃንክ እምልብሰ እልታሕ ወሰንዱን
እስከነ ሰሐቁ ላዕሌከ ሐራ ጲላጦስ መስፍን
ክርስቶስ ክቡር በቅድመ አይሁድ ምኑን
ክድነኒ እግዚኦ ልብሰ ተፋቅሮ ብርሃን
እስመ ፍቅር ተዓቢ እምኵሉ ሥልጣን
[መልክኣ ማኅየዊ ዘውእቱ መልክአ ኢየሱስ ካልእ]

ሰላም ለዕርቃንከ ዘአዕረቅዎ አይሁድ፤
እምልብሰ ምድራዊ ግዙፋነ ክሣድ፤
ዕሥራኤል እሙንቱ ሕዝብ ክቡድ፤
ተማኅፀነ በዕርቃንከ ከመ ትዕቀበነ ወልድ፤
አንተ አቡነ ወንሕነ ውሉድ። [መልክኣ ቅንዋት]

ቅዱስ ያሬድም በፋሲካው ድጓ እንዲህ ይላል
“ሰአሎ ዮሴፍ ለጲላጦስ ወይቤሎ
#ሀበኒ_በድኖ_ለኢየሱስ
#ከመ_እክድን_ዕቃርኖ_በልብስ
#ለዘከደነ_ዕርቃንየ_በዮርዳኖስ - ዮሴፍ ለጲላጦስ እንዲህ አለው፡- በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ስጠኝ”

ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንደ ሰብአ ሰገል ምንኛ እድለኞች ናቸው? የአምላኩን እርቃን የሚሸፍን የራሱን ዕርቃን የሚከድን ነው።

እነርሱስ ከመስቀል ለማውረድ በአዲስ መቃብር ለማኖር ዕርቃኑን ለመክደን ሰውነቱን ለመሸፈን ጠይቀው ተፈቀደላቸው!

ታዲያ እኛስ …



tg-me.com/orthodox1/13088
Create:
Last Update:

ቤተልሔም ፣ ዮርዳኖስና ቀራንዮ
በልደት ፣ በጥምቀትና በስቅለት
የአምላክ «መራቆት»
━━━✦༒༒✦━━━

መኑ ይሁበኒ ሥጋሁ ለኢየሱስ
ከመ እክድን ዕርቃኖ በልብስ
ለዘከደነ ዕርቃንየ በዮርዳኖስ

[ በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ማን በስጠኝ ?]

የዘፍጥረት መጽሐፍ ቀዳሚ መልእክት እንዲህ የሚል ነው «ወምድርሰ ሀለወት እምትካት ዕራቃ ☞ ምድር ግን ከቀድሞው ራቁትዋን ነበረች» ይህም ከአዝርዕት ከአትክል ከሰው የተራቆተች ሆና ባዶ ፣ ከንቱ ሆና ምድረ በዳ ነበረች ማለቱ ነው [ዘፍ ፩፥፪]

የፍጥረቱ አክሊልና የምድራችን ጌጥ ሆነን የተፈጠርነው እኛ የሰው ልጆችም ራቁትነታችን በብርሃን መጋረጃ የተሸፈነ ነበር ፤ ኋላ በበደላችን ምክንያት ከጸጋ ልጅነት ከአምላክ ባለሟልነት ስንርቅ ተራቁተን ቀረን እንጂ "አእመሩ ከመ ዕራቃኒሆሙ እሙንቱ ☞ ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ" እንዲል [ዘፍ ፫፥፮]

እግዚአብሔርን ለመምሰል ብርሃን ተጎናጽፎ ይኖር የነበረው ሰብእናችን በበደሉ ምክንያት ዕርቃናቸውን የሚኖሩ እንሰሳትን መሰለ።

አባ ጊዮርጊስ ይህን ርደት እንዲህ ገልጦታል ፦ “ምንት ውእቱ ተመስሎ እንስሳ ዘእንበለ ተከሥቶ ዕርቃኑ ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ሶበ ነፍጸ አጽፈ ብርሃን ዘላዕሌሁ ኀደጎ አጽፈ ብርሃን ⇨ በገነት ዛፎች መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ከመተየት በስተቀር እንስሳን መምሰል ምንድ ነው? የብርሃን ልብስ ከበላዩ ላይ በተገፈፈ ጊዜ የብርሃን መጐናጸፊየው ተለየው” (መጽሐፈ ምሥጢር)

በፍና ሠርክ በድምጸ ሰኮና ብእሲ ‘እንደምን ባለ አነዋዋር አላችሁ ይሆን ? በክብር ወይስ በኃሣር ? ’ እያለ ፈልጎ አገኘንና ስለመተላለፋችን ፈርዶ ከቀደመ ክብራችን አውርዶ ከገነት አስወጣን፤ ያን ጊዜ በጊዜአዊነትም ቢሆን ሐፍረት መክደኛ ዕርቃን መሸፈኛ አበጀልን! "ወገብረ እግዚአብሔር ለአዳም ወለብእሲቱ አእዳለ ዘማእስ ወአልበሶሙ … እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም።” [ዘፍ ፫፥፳፩]

ኋላ በምስጋና መብረቅ የተጋረደና በእሳት ደመና የተሸፈነ አምላክ ወልደ አምላክ የተስፋውን ቃል ለመፈጸም ከውድቀታችን ሊያነሳን ያን የተራቆተ ሥጋችንን ለበሰልን። የሚካኤል ሠራዊት በፍርኃት የገብርኤል ሠራዊት በመንቀጥቀጥ የሚያመሰግኑት እርሱ ዕርቃኑን በመካከላችን ተገኘ።

🍁 ወበቤተልሔም ወጽአ እምከርሰ እሙ ዕራቁ (በቤተልሔም ከእናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ)

መጽሐፍ "ዕራቅየ ወፃእኩ እምከርሠ እምየ" እንዳለ እኛን በሚመስልበት የተዋህዶ ግብር ከድንግል እናቱ ማሕፀን ዕርቃኑን ተወለደ፤ ከመለኮቱ ሳይራቆት (ዕሩቅ ብእሲ ሳይሰኝ) ከሥጋ ልብስ ባዶ ሆኖ ተራቁቶ ፣ ክብሩን በፈቃዱ ትቶ በትህትና ወደምድራችን መጣ። ይህን ሥጋችንን ለብሶ የሰው ልጅ መባሉ ያንን የሰማይ ክብር እርሱን በጸጋ ለብሰን ትርሲተ ወልድ / የሥጦታ ልጆቹ ሊያሰኘን ነውና።

የመጽሐፉም ምስክርነት እንዲህ የሚል ነው "አሰረቶ መንኮብያቲሁ ወአስከበቶ ውስተ ጎል ወጠብለለቶ በጽርቅት ⇨ አውራ ጣቱን አሰረችው ፣ በግርግም አስተኛችው፣ በመጠቅለያም ጠቀለለችው” [ሉቃ ፪፥፯]

የ፲፭ ዓመቷ ገሊላዊት ብላቴና እናቱ ድንግል ማርያም በከብቶቹ ማደርያ ስትወልደው ለብኩርናው አውራ ጣቱን አሥራ፣ የተራቆተ ሰውነቱን በጨርቅ ጠቅላላ ፣ ለመኝታው ግርግም አሰናድታ ባላትና ባገኘችው ተቀበለችው። ይህም ለእኛ የተከፈለው ካሣ እረኞችም ምልክት እንዲሆናቸው በመልአኩ በኩል ‘እሱረ መንኮብያት ፣ ስኩብ ውስተ ጎል ፣ ጥብሉል በአጽርቅት (አውራ ጣቱ የታሠረ ፣ ከግርግም የተኛ ፣ በጨርቅ የተጠቀለለ) ሕፃን በበረቱ ታገኛላችሁ’ ተባሉ። [ሉቃ ፪፥፲፪]

ልጇን ጌታዬ የምትል ብቸኛዋ የፈጣሪ እናቱ የአምላክ ወላዲቱ ለዕርቃኑ መክደኛ የበለስ ቅጠል ስላገኘችበት ተኣምራታዊ መንገድ በቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ትውፊት
እንዲህ የሚል አብነት አለ
«በለሶን ዕፀ አእምሮ የሚባለው ነው፤ ይህ የገነት በለስ አዳምና ሔዋን ፍሬውን በልተው ቅጠሉን የለበሱት ኋላም የልደት ዕለት በተኣምራት መልአክ (ቅዱስ ገብርኤል) አምጥቶላት ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ለልጇ ለዳግማይ አዳም ሥግው ቃል ክርስቶስ ያለበሰችው ነው፤ ቅዱስ ያሬድ በድጓው "ከደነቶ እሙ ቄጽለ በሰሶን" እንዳለው። ስለዚህ ምሥጢር ብዙዎች ብዙ ብለዋል!

ባለቅኔው ፦
በለሰ ገነት ለአዳም ወሔዋን መቲሮቶሙ
መንክረ ልደት አምላከ መንገሌሆሙ ሰሐበ
ወገብርኤልሃ ዜናዊ ቀጸበ
እንተ ከመዝሰ ግብር እምከመ ለአዳም ተውህበ
ወረከበት ሔዋን ዘኢተረክበ
ካዕበ ይስሐብ ኀቤሆሙ አበ
ለበለሰ ይምትርዎ ካዕበ

ደራሲው ፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ ዕሩያነ አካል ወአምሳል፥
አቅርንተ ነቢያት ሥላሴ ዘድምጽክሙ ወንጌል፥
ኢሳይያስ ጸርሐ ወይቤ ውስተ መካነ ላሕም ጎል፥
ገብርኤል አወፈየኒ ሕፃነ ማርያም ድንግል፥
በቆጽለ በለሶን ክዱን ወበጸርቅ ጥብሉል

🍁 ወበዮርዳኖስ ተጠምቀ በማይ ዕራቁ (በዮርዳኖስ ዕርቃኑን በውኃ ተጠመቀ)

ለኃጢዓታችን ሥርየት የሚሆን በግዕ ዘመስዋዕት፣ ለነፍሳችን ጠባቂዋ እረኛ ሊቀ ኖሎት፤ ወልዱ ለቡሩክ: ከሣቴ ብርሃን የዓለም መድኃኒት በባርያው በዮሐንስ እጅ እንዲጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ ሲገባ ከልብሱ መራቆቱን የአበው መጽሐፍ እንዲህ ይገልጣል

"አስተርአየ በውስተ ዮርዳኖስ እንዘ ክሡት ዕርቃኑ ለተጠምቆ ⇨ ለመጠመቅ ራቁቱን በዮርዳኖስ ባሕር ውስጥ ታየ" (መጽሐፈ ምሥጢር)

የዮርዳኖስ ጥምቀት የሁላችን ዕርቃን የተከደነበት ነው።

🍁 ወበቀራንዮ ሰቀልዎ ዲበ ዕፅ ዕራቆ (በቀራንዮ በእንጨት ላይ ዕርቃኑን ሰቀሉት)

አባ ጊዮርጊስ ስለዚህም እንዲህ ብሏል “ወበከመ ተከሥተ ዕርቃነ አዳም ማእከለ ዕፀዊሃ ለገነት ከማሁ ተከሥተ ዕርቃነ ትስብእቱ ለመድኃኒነ ማዕከለ ጉባኤሆሙ ለማኅበረ እስራኤል ⇨ አዳም በገነት ዛፎች መካከል ርቃኑን እንደታየ እንደሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በሰውነቱ በአይሁድ ጉባኤ መካከል ዕርቃኑን ሆኖ ታየ” (መጽሐፈ ምሥጢር)
በደራስያኑም የመልክእ ምስጋና እንዲህ ተገልጧል፦

ሰላም ለዕርቃንክ እምልብሰ እልታሕ ወሰንዱን
እስከነ ሰሐቁ ላዕሌከ ሐራ ጲላጦስ መስፍን
ክርስቶስ ክቡር በቅድመ አይሁድ ምኑን
ክድነኒ እግዚኦ ልብሰ ተፋቅሮ ብርሃን
እስመ ፍቅር ተዓቢ እምኵሉ ሥልጣን
[መልክኣ ማኅየዊ ዘውእቱ መልክአ ኢየሱስ ካልእ]

ሰላም ለዕርቃንከ ዘአዕረቅዎ አይሁድ፤
እምልብሰ ምድራዊ ግዙፋነ ክሣድ፤
ዕሥራኤል እሙንቱ ሕዝብ ክቡድ፤
ተማኅፀነ በዕርቃንከ ከመ ትዕቀበነ ወልድ፤
አንተ አቡነ ወንሕነ ውሉድ። [መልክኣ ቅንዋት]

ቅዱስ ያሬድም በፋሲካው ድጓ እንዲህ ይላል
“ሰአሎ ዮሴፍ ለጲላጦስ ወይቤሎ
#ሀበኒ_በድኖ_ለኢየሱስ
#ከመ_እክድን_ዕቃርኖ_በልብስ
#ለዘከደነ_ዕርቃንየ_በዮርዳኖስ - ዮሴፍ ለጲላጦስ እንዲህ አለው፡- በዮርዳኖስ እርቃኔን የሸፈነውን እርቃኑን በልብስ እሸፍን ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ ስጠኝ”

ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንደ ሰብአ ሰገል ምንኛ እድለኞች ናቸው? የአምላኩን እርቃን የሚሸፍን የራሱን ዕርቃን የሚከድን ነው።

እነርሱስ ከመስቀል ለማውረድ በአዲስ መቃብር ለማኖር ዕርቃኑን ለመክደን ሰውነቱን ለመሸፈን ጠይቀው ተፈቀደላቸው!

ታዲያ እኛስ …

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13088

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

How Does Bitcoin Mining Work?

Bitcoin mining is the process of adding new transactions to the Bitcoin blockchain. It’s a tough job. People who choose to mine Bitcoin use a process called proof of work, deploying computers in a race to solve mathematical puzzles that verify transactions.To entice miners to keep racing to solve the puzzles and support the overall system, the Bitcoin code rewards miners with new Bitcoins. “This is how new coins are created” and new transactions are added to the blockchain, says Okoro.

Export WhatsApp stickers to Telegram on iPhone

You can’t. What you can do, though, is use WhatsApp’s and Telegram’s web platforms to transfer stickers. It’s easy, but might take a while.Open WhatsApp in your browser, find a sticker you like in a chat, and right-click on it to save it as an image. The file won’t be a picture, though—it’s a webpage and will have a .webp extension. Don’t be scared, this is the way. Repeat this step to save as many stickers as you want.Then, open Telegram in your browser and go into your Saved messages chat. Just as you’d share a file with a friend, click the Share file button on the bottom left of the chat window (it looks like a dog-eared paper), and select the .webp files you downloaded. Click Open and you’ll see your stickers in your Saved messages chat. This is now your sticker depository. To use them, forward them as you would a message from one chat to the other: by clicking or long-pressing on the sticker, and then choosing Forward.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from pl


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA